Monday, April 28, 2014

መለስ ዜናዊ ኤርትራን ለማስገንጠል ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሃፊ የጻፈው የተማጽኖ ደብዳቤ

መለስ ዜናዊ  ኤርትራን ለማስገንጠል ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሃፊ የጻፈው የተማጽኖ ደብዳቤ

TRANSITIONAL GOVERNEMENT OF ETHIOPIA OFFICE OF THE PRESIDENT
13 December 1991
Excellency, Mr. Secretary-General,
As your Excellency is well aware, the transitional government period in Ethiopia highlights the task of redressing the causes of the 30-year civil war in Eritrea and of establishing the basis of permanent peace and stability.
It is to be recalled that the conference on peace and Democracy in Ethiopia, held in Addis Ababa from 1-5 July 1991, adopted a charter affirming that freedom, equal rights and self-determination of all peoples are the cardinal principles governing state affairs in new Ethiopia. In light of this, the conference formally recognized that the people of Eritrea have the right to determine their own future themselves and accepted that the future status of Eritrea should be decided by the Eritrean people in a referendum to be conducted in the presence of international observers. The provisional Government of Eritrea set by EPLF, on its part, decided to deter the referendum for two years which, we believe, contributes to the maintenance of peace and stability in our sub-region. At the same time, agreement was reached on the modalities of relationship between the Transitional Government of Ethiopia and the Provisional Government of Eritrea for the interim period.
Both the transitional Government of Ethiopia and the Provisional Government of Eritrea have registered their commitments to respect the results of the referendum in Eritrea as the genuine choice of the people concerned, expressed in an exercise of self-determination.
The Transitional Government of Ethiopia, as an interested party in the outcome of the referendum, has the firm conviction that the referendum will be free and fair, and believes that the United Nations should play an active role in verifying that the referendum is, indeed, fair and free.
In this regard, the Transitional Government of Ethiopia wishes to bring the attention of your Excellency the need to *………………… ………………… …………… ……………………… ………………………  * to play this role and make the necessary arrangements with the Provisional Government of Eritrea   to facilitate the ways and means for the UN supervision of the referendum. The Transitional Government of Ethiopia also wishes to point out that the time available for preparation in this regard is very short.
With highest considerations,
Signature
Meles Zenawi
President of the Transitional
Governement of Ethiopia
H.E. Javier Peraz de Cuellar
Secretary-General of the United Nations
UN Headquarters
NEW YORK

ዜጎች በጎጃም መሬቸውን እየተነጠቁ ሲሆን፤ በምስራቅ ወለጋ ስቡ ስሪ ወረዳ ደግሞ ‹‹ይህ አገር የእናንተ አይደለም፡፡ አገራችሁን ግቡ፡፡›› በሚል 200 ያህል አርሶ አደሮች እንደተፈናቀሉ አስታወቁ፡፡ የወያኔ ግፍ መቼ ይሆን የሚያበቃው?

ዜጎች በጎጃም መሬቸውን እየተነጠቁ፤ በወለጋ ደግሞ እየተፈናቀሉ ነው!

map

አርሶ አደሮች መሬታቸውን ያለካሳ እየተነጠቁ ነው

መራዊ፡- በምዕራብ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ ያለ ፈቃዳችን መሬታቸውን አሳልፈን አንሰጥም ያሉ አርሶ አደሮች እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ በመራዊ አካባቢ ሜጫ ወረዳ እናሸንፋለን ቀበሌ መንግስት የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ እናካሂዳለን በሚል ከ400 በላይ የሚሆኑ አርሶ አደሮች ከመሬታቸው እንዲለቁ የተደረገውን እርምጃ አርሶ አደሮቹ በመቃወማቸው እስርና ድብደባ እየደረሰባቸው መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
በአካባቢው ከአሁን ቀደም ተመሳሳይ እርምጃዎች የተወሰዱ ሲሆን የአርሶ አደሮቹ መሬት በአበባ ኢንቨስትመንት ላይ ለተሰማሩ ባለሀብቶች ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ይህም በአሁኑ ወቅት መንግስት ውሃ ለመቆፈር በሚል አርሶ አደሮቹ ከመሬታቸው እንዲለቁ የሚወስደው እርምጃ በተመሳሳይ ለአበባ እርሻ ሊሰጥባቸው እንደሆነ በማመናቸው ከመሬታቸው አንለቅም ብለዋል፡፡ እስካሁን ለአበባም ሆነ ለሌሎች ተግባራት መንግስት ከአርሶ አደሮቹ መሬት ሲወስድ ያለ ምንም ካሳ በመሆኑ አርሶ አደሮቹ አሁንም ቢሆን ያለ ካሳና ያለምንም ፈቃድ እየተነጠቁ በመሆኑ ተቃውሟቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አድርጓዋል፡፡
ከአርሶ አደሮች ባሻገር በከተሞች የሚኖሩ የአርሶ አደሮቹ ቤተሰቦች ጭምርም ችግር እየደረሰባቸው መሆኑን ምንጮች ጨምረው ተናግረዋል፡፡ በተለይም ታሳሪዎቹን የሚጠይቁት የአርሶ አደሮቹ ቤተሰቦችና ሌሎች የአካባቢውና በየከተማው የሚኖሩ ግለሰቦችም ለእስር መዳረጋቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ አርሶ አደሮቹ መሬታቸውን ያለ ፈቃዳቸው አሳልፈው እንደማይሰጡ በመግለጽ ጠንካራ ተቃውሞ ማንሳታቸውን ተከትሎ በአካባቢው ፖሊስና መከላከያ በብዛት መሰራጨቱን ምንጮች አክለው ገልጸዋል፡፡

በምስራቅ ወለጋ ዜጎች እየተፈናቀሉ ነው

በምስራቅ ወለጋ ስቡ ስሪ ወረዳ ‹‹ይህ አገር የእናንተ አይደለም፡፡ አገራችሁን ግቡ፡፡›› በሚል 200 ያህል አርሶ አደሮች እንደተፈናቀሉ አስታወቁ፡፡
በ1990ዓ.ም ጀምረው በአካባቢው የኖሩት እነዚህ ዜጎች ‹‹የመኖሪያ መታወቂያ ተሰጥቶን፣ውጡ ተብለን እየታሰርንና እየተባረርን እንኳ ግብር እያስከፈሉን፣ ንብረት አፍርተን አገራችሁ አይደለም ተብለን እየተፈናቀልን ነው›› ሲሉ ምሬታቸውን ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡ አርሶ አደሮቹ ከዚህ ቀደም በ1992 በተመሳሳይ ቤትና ንብረታቸው ወድሞ ተፈናቅለው የነበረ ቢሆንም መንግስት እንደገና እንዳቋቋማቸው ይገልጻሉ፡፡
‹‹በአንድ በኩል አገራችሁ አይደለም ውጡ!›› የሚሉት የአካባቢው ባለስልጣናት በሌላ በኩል ደግሞ ‹አካባቢውን ልንሰራበትና ልናሰራበት ነው ይሉናል፡፡ በ1992ም መንግስት እንደገና አቋቁሞናል፡፡ አሁንም ቦታው ከተፈለገ መንግስት ተገቢውን ካሳ ሊሰጠን ይገባል፡፡› ብለን ስንጠይቅ ደግሞ ‹እናንተን መንግስት አያውቃችሁም፡፡ ይሉናል› በሚል እየደረሰባቸው ያለውን ህገ ወጥ ተግባር ይናገራሉ፡፡
ተፈናቃዮቹ ከጥር 22 2006 ዓ.ም ‹‹ለቃችሁ ውጡ፡፡ ለቃችሁ ካልወጣችሁ ለቤትና ንብረታችሁ ብቻ ሳይሆን ለህይወታችሁም ኃላፊነት የላችሁም›› መባላቸውን ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ተደጋጋሚ እስራትና ድብደባ እንደደረሰባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
‹‹ለቃችሁ ውጡ!›› በተባሉበት ወቅት አቤቱታ ሲያቅረቡ የነበሩ 42 ሰዎች ያለ ምንም ምግብ ለ30 ቀናት ታስረው መቆየታቸውንና በየጊዜው ፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ ከቀያችን ተፈናቅለን፣ ልጆቻችን ትምህርታቸውን አቋርጠው፣ በችግር ላይ እንገኛለን የሚሉት ተፈናቃዮቹ ‹‹ሀገርና ተቆርቋሪ የሌለን ዜጎች ሆነናል፡፡ ከ16 አመት በላይ የኖርንበትን ቀያችን ለቀን ወደ የት እንሂድ? የሚመለከታችሁ አካላት ሁሉ በተግባር እርዱን›› ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ (ምንጭ፡ ነገረ ኢትዮጵያ)

Sunday, April 27, 2014

የህዋሃት መሪዎች ፋሽስታዊ ተፈጥሮ ሲጋለጥ

የህዋሃት መሪዎች ፋሽስታዊ ተፈጥሮ ሲጋለጥ
(አስገደ ገ/ስላሴ፣ መቐለ)

 ህ.ወ.ሃ.ቶ.ች በ 1983 ዓ/ም ስልጣን እንደያዙ ልክ ፋሽስታዊ ደርግ ‘ኢትዮጵያ ትቅደም ያለ ምንም ደም ብሎ!’ የኢትዮጵያ ህዝብ ልብን ለመግዛት እንደሞከረ ሁሉ የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎችም ስልጣን ከያዙ በኋላ የተቆጣጠሩት መገናኛ ብዙሃን የደርግን ክፋት በመለፈፍ እንዲጠመዱ፣ ባንጻሩ የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች ጀግነትና መልካምነት አጋነው እንዲዶሰክሩ ተደርገው ነበር።

ሁሉም አይነት ሰብአዊ መብቶች የህግ የበላይነትን እናረጋግጣለን ብዙሃን ፓርቲ ነፃ ሆነዉ እንዲቀሳቀሱ ነፃ ምርጫ በማድረግ በሰላማዊ መንገድ የስልጥን ሽግግር እናደርጋለን በማለት ለጊዜዉ ሁሉም ፓርቲዎች የሚሳተፉበት የሽግግር መንግስት አብዛኞቹ ራሱ የጠፈጠፋቸዉ ፓርቲ በማሳተፍ ሽግግር መንግስት መሰረተ ቆየት ብሎም ህገ-መንግስት አርቃቂ ኮሚሽን አቋቋመ ህግ-መንግስቱ አቶ ክፍለ ወዳጆ ብዙ የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች ተፅእኖ በተቻላቸዉ በመከላከል ደሀና ሊባል የሚችል በወረቀት ደረጃ ተዘጋጀ ህገ-መነገስት በዋናነት ያተኩርበት የነበረ በተለይ የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች በተለይ ደግሞ መለስና ጓዶቹ የኢትዮጵያ ሉአላዊነት የሚደፍርና ባሀር የሌላት በመሬት የተዘጋች አገር ለመመስረት ጠንክረዉ ይታገሉ ነበር። በዛን ወቅት እንደነ ኢ.ህ.አ.ፓ የመሳሰሉ አንጋፋ ፓርቲ ደርግን ለመጣል አነስተኛ የማይባል አስተዋፅኦ የነበራቸው ለማግለል ዋና ጥረት ነበር ኦ.ነ.ግ.ም ከሽግግሩ መንግስት እንዲወጣ ተደረገ። በቃ በኢትዮጵያ የህ.ዋ.ሃ.ት መሪዎች የነበረ ጉራና ውሸት ሳይጎረምስ አረጀና ገና በጥዋቱ የህ.ዋ.ሃ.ት መሪዎች አስተሳሰብ ያልተቀበለ ሁሉ ጥይት አጉርሰዉ ማለት ጀመረ ኢ.ህ.አ.ፓ ኦ.ነ.ግ ተመቱ ሌሎች አነስተኛ ፓርቲዎች ወደ ስልጣን ያወጡዋቸዉ የህ.ወ.ሃ.ት ታጋዮችም ከ 32000 ታጋዮች በላይ አሰሩዋቸዉ ደብዛቸዉ አጠፍዋቸዉ ኣበረርዋቸዉ በትግራይ ክልል ከተማና ገጠር ነዋሪዎች ህዝብም ስለ ኤርትራ ሪፈረንደም ስለ የባሀር በር ስለ ዲሞክራሲያዊና ሰብኣዊ መብት ስለምልካም አስተዳደር ጥያቄ ያነሱ ወገኖች ታሰሩ ከቀላል እስከ ከባድ ቅጣት ተቀጡ ነፃ ፕሬስ ተዘጉ ወይ እንደ ጠላቶች ታዩ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ በማድረግ ዲሞክራስያዊ ህዝባዊ መንግስት እንመሰርታለን የሚል ጉራና ውሸት ህልም ሆኖ ቀረ። ነፃ የተቀዋሚ ፓርቲ እንቅስቃሴ በድህንነት እጅ ገባ። የህግ የበላይነት ለህዝብ መሆኑ ቀርቶ በህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች እጅ ወድቆ እስከ አሁኑም አቃቤ ህግ ድህንነት ሁሉ ለህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች ጠባቂና ህዝብን ማፈን ዋና ስራቸው ሆኖም ይገኛል፣ ዳኞችም ነፃነታቸው የተጠበቀ አይደለም የህግ ጠበቃዎም በህ.ወ.ሃ.ት አመራር አይን በጠላትነት ተፈርጀው የዳኝነትን ውሳኔዎች እንደ አፍራሽ ጠላት ሆነው ተፈርጀዋል።

 በአጠቃላይ የመንግስት ሰራተኞች መምህር፣ሃኪም፣ተማሪ፣ የዩንቬርስቲ ህ/ሰብ ከህ.ወ.ሃ.ት አመራር ውጭ የሚያስቡ የህ.ወ.ሃ.ት
ፓርቲ አባል ያልሆኑ በጠላትነት ይታያሉ።ትምህርት ቤት ከ4 ኛ ክፍል እስከ ዩንቨርስቲ ያሉ አንድ ለአምስት በመደራጀት በህ.ወ.ሃ.ት ፈሽስታዊ ባህርያት እየታነፁ ፀረ ዲሞክራሲ ስራ በመፈፀም እንዲሰለፉ አየተደረገ ነው። በሕ/ሰቡ ውስጥ በሱስ የደነዘዙ፤ የተጠሉ ምንም ሰብአዊነት የሌላቸው ወጣቶችና ህፃናት የህ.ዋ.ሃ.ት መሪዎች በገንዘብ እየደለሉ ህግ-መንግስትን አክብረዉ የሚታገሉ ፓርቲዎችንና ወገኖች በድንጋይ እንዲደበደቡ በማድረግ ደማቸዉ በጎዳና እየጎረፈ ይታያል ታስረዋል ካሜራቸውንና ሞባይላቸውን ተቀምተዋል። ለዚሁ እንደምሳሌ ለማሰቀመጥ በአዲግራት አፅቢ ወንበርታ በእንደርታ ወረዳ እድሜአቸዉ ከ3 እሰከ 12 አመት ህፃናት ለዓረና መድረክ አባላት ደብድበዋል የዜጎች /የታጋዮች ደም/ በአስፓልት ጎዳና/ፈሰዋል በተምቤን ዓበይ ዓዲ በሃገረሰላም በውቕሮ በሕሞራ በሽሬ በማይጨዉ በመቐለ በአላማጣ በዓድዋ ህዝብ የተቃዋሚዎች አማራጭ ሃሳብ እንዳይሰማ ወደ ስብሰባ እንዳይሄድ በፖሊሶች በደህንነት በቀበሌ ባንዳዎች በየቤቱ ጥበቃ ንዳይወጡ ተደርጓል። ያንሁሉ አፈና ጥሰዉ ወደ ስብሰባ የገቡ ዜጎች ከስብሰባ በኃላ ባለስልጣናት እየጠሩ ምክንያት እየፈጠሩ ማሰር ሌላዉ ቀርቶ የቀበሌ መታወቂያ መከልከል ዜግነታቸዉ መንጠቅ ይታያል። የፓርቲ ኣባላትም መታወቂያ እንዳይታደላቸዉ ተደርጓል ለምሳሌ መጥቀስ አያሌዉ በየነ ትውልድ ቀዬዉ አክሱም ውቕሮ ማራይ ወረዳ በውቕሮ ወረዳ በውቕሮ ከተማ ቀበሌ የሚኖር መታወቂያ አናድስልህም ተብሎ ለ4 አመት እየተሰቃየ ይገኛል። ለማረጋገጥ የሚፈልጉ ብዙሃን መገናኛ በ ስ.ቁ 0914 19 17 19 ጠይቁት።

በፋሽስታዊ ህወሃት አመራርና ባሁኑ ጊዜ ሲታይ ባሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የሚገኙ ተቃዋሚ ፓርቲ እንቅስቃሴ በተለይ ደግሞ በመድረክ ኣባላት የሆኑ የዓረና ትግራይና የአንድነት ፓርቲ በሰሜን ኢትዮጵያ የሚያደርጉት አማራጭ ሃሳባቸውን ወደ ገጠርና ከተሞች ዘልቀዉ ያደረጉት እንቅስቃሴ ለህ.ዋ.ሃ.ት ፋሽስታዊ መዋቅር / መርበብ/ በጣጥሰዉ ያሳለፉት መልእክት ሁሉም ህዝብ ስለተቀበላቸዉ በተለይ ደግሞ የህ.ዋ.ሃ.ት ፋሽስታዊ መሪዎች እንደመደበቂያ ዋሻ ሲጠቀሙበት የነበረዉ የትግራይ ህዝብ አሁን በህ.ዋ.ሃ.ት አመራር ፋሽስታዊ ተግባር ስለመረረዉ አልፎ አልፎም ለወረዳና ለቀበሌ አመራር ማመፅ ለከፍተኛ የክልሉና የህ.ዋ.ሃ.ት አመራር መሳደብ መናቅ ስለጀመረ እጅጉን ስላሳሰባቸዉ በጭንቀት ላይ ይገኛሉ። ይህን ጭንቅ ለመፍታት - ስዩም መስፍን የሚመራዉ ቡድን በቅርብ በብራስለስ እየታከሙ ነዉ ተብሎ ሲነገርለት የቆየዉ ስብሃት ነጋ አባይ ፀሃዬ ሃለቃ ፀጋይ በርሀ ከራያ እስከ ሽሬ ያሉ ከተሞችና የገጠር ነዋሪዎች በመንቀሳቀስ ስልጣን ጣፋጭ ነውና ወደ ህዝብ እየዞሩ በተለይ ደግሞ ዓረና ትግራይ
ሰፊ እንቅስቃሴ ያደረገባቸዉ ከተሞችና ገጠር ግለሰቦች በማግኘቴ ለመነጋገር እንኳን ቢፈልጉ የስድብ ናዳ እየወረደባቸዉ ስላለ
ሸሽተዉ ወደ መቐለ ተመልሰዉ እስከ አሁን አላማዉ ያልታወቀ ከመላዉ ትግራይ ቀበሌ፣ ወረዳ፣ ዞን አመራርና ልዩ ካድሬዎች ደህንነት በሚያደርጉት ዝግ ስብሰባ ( ኮንፍረንስ) በመሳተፍ ህዝብ ስለከዳን ለምርጫ 2007 ዓ/ም እንዴት አድርገን ድምፁን እንዲሰጠን እናድርግ በማለት በሃወልት ሰማእታት ፣ በፕላኔት ሆቴል በሚላኖ ሆቴል አዳራሾች በስብሰባ ላይ ተጠምደዉ ይገኛሉ።

- ሁሉንም ሰዉ ያስገረመዉ ግን በትግራይ ክልል በብዙ ሺ የሚቆጠር በሙስና የናጠጡ ካድሬ እያለ እነ ስዩምና ስብሃት ነጋ ኣባይ ፀሃዬ ፀጋይ በርሀ ሌሎችም ወደ ቀበሌ ወርደዉ ከህዝብ ጋር ለመታረቅ ጥረት ማድረግ ምን ያህል የህ.ዋ.ሃ.ት አመራር ከአባላቱ እንደተነጠሉና በመዋቅሩ እምነት እንዳጣ የሚያሳይ ነዉ።ይህ ደግሞ ፋሽስቶች ማንነታቸዉ በህዝብና በማዋቅራቸዉ ታውቀውና ተንቀዉ ውድቀታቸው ሲደርስ ተስፋ ቆርጠዉ ራሳቸዉ ወርደዉ እንደ ተራ ካድሬ ዲስኩር ያሰማሉ ይህ ተግባር ቀደም ሲል በሂትለርና በመሶለኒ ታይቷል። ትናንትም በመንግስቱ በጋዳፊ ወ.ዘ.ተ ታይቷል። የህ.ዋ.ሃ.ት ፋሽስታዊ አመራር የአጎቶቹ የነመንግስቱ እጣ አጋጥሞት ከዛ በላይ ካከዳዉ እየተጋጨ እነዚህ የ 70 እና የ80 አመት አዛውንት ፋሽስታዊ አገዛዛቸዉ እንዳይነጠቁ በዚህ በአብይ ፆም ሃይለኛ ፀሃይ ብቻቸውን እያበዱ ይግኛሉ።
- ከህዋሃት መንደር ምንጮች እንደሚያናፍሱት የህ.ዋ.ሃ.ት አመራር ከቁንጮ እስከ ቀበሌ ታማኝነታቸዉ ከህዝብ ስላጡ አሁን
የመላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ መልካም አስተዳደር ፍትህና ነፃነት ስላጣ ባለስልጣናት በሙስና ስለተበላሹ ታማኝነታቸውን ወደ ዜሮ
ስለወረደ በህዝብ ታማኝነት ልናገኝ ከተፈለገ ህዝቡን አሳማኝ የሆኑ ከሙሰኞች ከፀረ-ዲሞክራሲ ጫፎች እያለፍን እንምታ ብለዉ
ድምዳሜ ላይ እንደደረሱ ምንጮች ይናገራሉ በመሆኑመ በኣሁኑ ጊዜ የህ.ዋ.ሃ.ት ፋሽስታዊ መዋቀር በፍርሃት እየተናጠ ይግኛል።
- አሁን የሚያስቡት የማተለል ስልት በትግራይ ህዝብ በገበሬዉ በምሁሩ በባለሃብት በነጋዴዉ ምንም አይነት ተቀባይነት የለዉም 23 አመት ሙሉ እንደ እስስት እየተቀያየሩ እንደቀበሩት ስለተረዳ ነዉ
- ምናልባት አንዳንድ ወገኖች የህ.ዋ.ሃ.ት አመራር ፋሽስታዊ ባህርያት ዛሬ ነዉ የተከሰተዉ ትሉ ይሆናል በበኩሌ ህ.ዋ.ሃ.ት
ከተፈጠረበት ዘመን ጀምሮ ከህ.ዋ.ሃ.ት ፖለቲካ እምነቶች ውጭ ሌላ ሃሳብ የሚያራምዱ ሃሳቤን ያላመነ ጥይት ኣጉርሰዉ እያለ እንደመጣና
ብዙ ፓርቲዎች ግልሰቦች እየዋጠ እንደመጣ በተለያዩ ጊዜያት ግልፅ አድርጌ ነበር።
- ከ 1983 እና ከዛ በኃላ የነበሩት ጊዜያት ግን ምንም እንኳን እንደነ ሂትለርና መንግስቱ ነጋሪት ባይጎስም ጥሩምባ ባይነፋም በተግባር ግን ብዙ ፖለቲካ ፓርቲ እጅግ ብዙ ጋዜጠኞች በዙ ምሁራን እንዲጠፉ እንዲሰደዱ እንዲታሰሩ እንዲቀጡ አድርጓል። የሃገራችን ሃብትም በሙስና ተበልቷል ተመዝብሮ ውጭ አገር ሰፍሯል። የህ.ዋ.ሃ.ት አመራር በሃገራችን የሌለ ዲሞክራሲ አለ የሌለ ብልፅግና በልፅጓል ብሎ ዋሽቷል የህዝባችን ታሪክ አበላሽተዋል ሉአላዊነት ሃገር ተደፍረዋል መሬታችን የባህር በራችን አሳጥቷል 90 ሚሊዮን ህዝብ የመሬት ባለቤትነቱን አጥቶ ዜግነቱ ተነጥቀዋል ታዲያ የህ.ዋ.ሃ.ት ኢ.ህ.አ.ደ.ግ አመራር ዘመናዊ ፋሽስት ከማለት ውጭ የተሻለ ስም ምን እንስጠዉ። ምክንያቱም ተደብቆ ቆይቶ ተደማምሮ ፋሽስታዊ ተፈጥሮዉ ሊደብቅ ቢፈልግ መደበቂያ ዋሻ አይገኝለትም። ይልቁንም የህ.ዋ.ሃ.ት መሪዎች ፋሽስታዊ ጎርፍ አፍሶ እንዳያጠፋን ሁሉም የኢትዮጵያ ህዘብ በመተባበር የጥንት ወላጆቹ ጠብቀውት በቆዩት ሃገር ሉአላዊነት አንድነት ፍቅርና መተሳሰብ ያስፍን የህ.ዋ.ሃ.ት መሪዎችና ስሪታቸዉ የሆኑ አባላት በታኝና ከፋፋይ ስርአት ከእንግዲህ ይቁም

ከሰላምታ ጋር

አስ ገደ ገ/ስላሴ፣ መቐለ

የፌደራል ፖሊስ በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ቶክስ ከፈተ። ቁጥራቸው ያልታወቁ ተማሪዎች ተጎድተዋል። ጂማ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው ተመሳሳይ ተቃውሞ ከ 10 በላይ ተማሪዎች ታስረዋል። አምቦም እንዲሁ ከ 15 በላይ መታሰራቸው ይታወሳል።

Ethiopian Security Forces Open Fire on Students

Friday, April 25, 2014

የ“ህዳሴው” ግድብ ተጽዕኖ ሌላ አቅጣጫ መያዙ አሳሳቢ ሆኗል

የ“ህዳሴው” ግድብ ተጽዕኖ ሌላ አቅጣጫ መያዙ አሳሳቢ ሆኗል

የአቡነ ማቲያስ የግብጽ ጉብኝት ላልተወሰነ ጊዜ ተላልፏል
abay and church
ሃያ አምስት በመቶ እንደተጠናቀቀ የሚነገርለት የ“ህዳሴው” ግድብ በኢትዮያና በግብጽ መካከል ከፈጠረው የፖለቲካ ቁርቋሶ በተጨማሪ ወደ ሃይማኖት መንደርም እየዘለቀ ነው፡፡ ዛሬ (አርብ) ግብጽን ለመጎብኘት ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበሩት አቡነ ማቲያስ ከግብጽ በኩል እንዳይመጡ በተላለፈላቸው መልዕክት መሠረት ጉብኝታቸውን ላልተወሰነ ጊዜ አስተላልፈውታል፡፡
በግብጽና በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የተለያዩ የዜና ዘጋቢዎች እንዳሉት ከሆነ መልዕክቱ ያስተላለፉት የግብጹ ፓትሪያርክ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ ናቸው፡፡ ፓትሪያርኩ ለአቡነ ማቲያስ ባስተላለፉት መልዕክት በበርካታ ቢሊዮን ዶላር የሚገነባው የአባይ ግድብ የፈጠረው ሁኔታ እንዳለ ሆኖ ይህንን ጉብኝት ማካሄድ የግብጽን ቤ/ክ “የሚያሳፍር” ይሆናል በሚል ነው ምክራቸውን ለአቡነ ማቲያስ የለገሱት፡፡
ስማቸውን ሳይጠቅሱ መረጃውን ለግብጽ የሚዲያ አካላት የተናገሩት ባለሥልጣን እንደሚሉት ከሆነ ሁለቱ ቤ/ክናት ለረጅም ጊዜ የቆየ ግንኙነት ቢኖራቸውም ግድቡን በተመለከተ ይፋዊ ያልሆነ ሽምግልና የማካሄዳቸው ሁኔታ የማያዛልቅ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሁለቱ ከፍተኛ የቤ/ክ መሪዎች በሚገናኙበት ወቅት ይህ ጉዳይ ሳይነሳ እንደማይታለፍ የታወቀ ነው፡፡
አቡነ ታዋድሮስ “አሳፋሪ” ያሉትን ጉዳይ በዝርዝር አልገለጹትም ሆኖም የግድቡ መሠራት ግብጽን ክፉኛ ያሳሰባት ጉዳይ ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ በተለያዩ ጉዳዮች ውስጥ ጣልቃ ስትገባ ከመቆየት አልፋ ኢህአዴግን ለሚቃወሙ የመሣሪያና የመሳሰሉ ዕገዛዎችን ለማድረግ ስትንቀሳቀስ መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡
በሃይማኖቱ ዓለም ከፍተኛ ትስስር ያላቸው የግብጽና የኢትዮጵያ ቤ/ክናት ከ“ህዳሴው” ግድብ ጋር በተያያዘ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳቸው የውጥረቱን አሳሳቢነት የሚገልጽ ነው የሚሉ ክፍሎች ግብጽ መረጋጋት ስታገኝ የሚሆነውን ለመተንበይ ያስቸግራል ይላሉ፡፡ የሃይማኖት ተቋማት ለዕርቅና ሰላም መሥራት በሚገባቸው ጊዜ ከፖለቲካው በላይ መሆን አለመቻላቸው ሹመታቸውም ከዚያው የመነጨ ለመሆኑ ማስረጃ ነው፡፡ አገልግሎታቸውም ከፖለቲካው ሥልጣን በላይ መሆን ያልቻለ መሆኑን በግልጽ ያሳያል በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ፡፡
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ያነጋገራቸው ባለሙያ እንደሚሉት የግድቡ ሥራና በሁለቱ አገሮች መካከል የተፈጠረው ሁኔታ ሁሉንም ሊያሳስብ የሚገባ ነው ይላሉ፡፡ በተለይ ኢህአዴግ የግድቡን ሥራ ለፖለቲካ መጠቀሚያነት ማዋሉ “አስከፊ ነው” ብለዋል፡፡ “አባይን የመገደቡ ጉዳይ አሁን የታሰበ ወይም የተጀመረ አይደለም፤ በንጉሡ ጊዜም ሆነ በደርግ ጊዜ የነበረ ነው፡፡ እኔ የፖለቲካ ተንታኝም ሆነ የታሪክ ምሁር አይደለሁም ነገር ግን በግድቡ ሥራ ላይ ባለኝ ሙያ በከፍተኛ ደረጃ እሳተፋለሁ፡፡ ህወሃት እና ኢህአዴግ ለራሳቸው ርካሽ ፖለቲካ መጠቀሚያነት ሲያውሉትና ሕዝቡን ከንቱ በሆነ አገራዊ ስሜት አስገብተው የራሳቸውን ፖለቲካ ለማራመድ የሚያደርጉትን ሁሉ በየቀኑ በሥራችን ላይ የምናየው አስከፊ ልምምድ ነው፡፡ እኔ የትግራይ ተወላጅ በመሆኔ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያዊነቴ አባይ ለዚህ መዋሉ ያስደስተኛል ነገር ግን ኅብረተሰቡ ሲጠይቅ “የግብጽ ደጋፊ ነህ፤ ጸረ-ልማት ነህ ወዘተ” ማለቱ የትም አያደርስም፡፡ በዚህ ላይ ከአገሪቷ ኢኮኖሚ አኳያ የግድቡ ወጪም ሆነ፣ የባለቤትነቱ ጉዳይ እንዲሁም ሌላ በርካታ ጉዳዮች ሊጠየቁ የሚገባቸው ጥያቄዎች ናቸው” ብለዋል፡፡
ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ዕቅድ ተይዞለት የነበረው የአቡነ ማትያስ የግብጽ ጉብኝት ላሁኑ ተላልፎ የነበረ ሲሆን የአቡነ ታዋድሮስ የመስከረም ወር የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውም በተመሳሳይ ምክንያት መሰረዙ ይታወሳል፡፡

"አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ህዝብ ነው።" አልጃዚራ ነው የዘገበው።

አማራ ከኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ከአፍሪካም እጅግ ድሃ ህዝብ ነው

በሰሜን ጎንደር ጭልጋ ከተማ አቅራቢያ በምትገኝ የገጠር ቀበሌ በአካባቢው ገበሬዎች እና በፌደራል ፖሊስ መካከል በተነሳ ግጭት የብዙ ሰዎች ህይወት ሲቀጠፍ ብዙዎችም ከባድና ቀላል ቁስለኛ ሆነዋል። ባጠቃላይ 11 መኪኖች ቁስለኛ እና አስከሬን ጭነው ማለፋቸውም ተረጋጧል።

ከሰሜን ጎንደር ጭልጋ ከተማ የደረሰኝ መረጃ  | Zehabesha Amharic

Thursday, April 24, 2014

የሰማያዊ ፓርቲ አባል በሙስሊምነቱ ተከሰሰ | Zehabesha Amharic

የሰማያዊ ፓርቲ አባል በሙስሊምነቱ ተከሰሰ | Zehabesha Amharic

የወታደራዊ መኮነኖች ቅነሳ?! ህወሓት እየተዳከመ መሆኑ የሚያሳይ ሌላ ማስረጃ ደግሞ በተለያዩ ክልሎች ይሰሩ የነበሩ የህወሓት የደህንነት ሰዎች ከያንዳንዱ ክልል መባረራቸው ነው!

የወታደራዊ መኮነኖች ቅነሳ?! ህወሓት እየተዳከመ መሆኑ የሚያሳይ ሌላ ማስረጃ ደግሞ በተለያዩ ክልሎች ይሰሩ የነበሩ የህወሓት የደህንነት ሰዎች ከያንዳንዱ ክልል መባረራቸው ነው!

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ታዋቂዋ የህሊና እስረኛ ሪዮት አለሙ በቃሊቲ እስርቤት በከፍተኛ ህመም እየተሰቃየች ስለሆነ የተባበሩት መንግስታት እና የአፍሪካ ህብረት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እንዲሁም አምነስቲ አለማቀፍ የሰባዊ መብት ትሟጋች እሷን ለማስፈታት ጥረት እንዲያደርጉ በጥብቅ አሳሰቡ።

AN URGENT APPEAL – From Mesfin Wolde-Mariam

The UN Human Rights Commission
The African Union Human Rights Commission
The International Red Cross
Amnesty International
Human Rights Watch
And
All Men and Women of GOOD WILL
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu is a budding Ethiopian poet, essayist, and journalist. There are not many Ethiopians of her caliber inside the country. She has been languishing in the famous Ethiopian Prison in Qalliti for almost three years. She was charged of terrorism, a crime she totally abhors. She was sentenced first for eighteen years but later reduced to three.
With the exception of her mother and father, she is not allowed to communicate with anyone, including her sisters, brothers as well as her fiancée.
Reeyot, although constantly in agonizing pain and in need of help, is held in solitary confinement with a very old and sickly foreign woman who herself requires assistance.
Reeyot is suffering from some growth in her breasts. The prison authorities have been reluctant to take her to hospital for medical checkup, even when her parents were prepared to pay the bill. When she became seriously ill she was allowed to see a doctor as a result of which she was taken to the hospital and operated upon. But no sooner had the surgeon finished the operation than she was immediately taken back to prison even before she had fully recovered from the Anastasia.
She now suffers from a relapse on the operated breast and similar growth in her other breast. The prison authorities still demonstrate their reluctance to provide medical treatment even at the expense of her parents.
May God provide the necessary courage to all those institutions and organizations to cry out effectively for this young lady who is suffering at the hands of insensitive prison administration.

Tuesday, April 22, 2014

"ወያኔ ኢህአዴግ ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡" አንድነት ፓርቲ።

ካልገደሉ አያቆሙንም – ሃብታሙ አያሌዉ (የአንድነት አመራር) ሰልፉን በተመለከተ


ሀገር የመገንጠል ዓላማ ይዞ የተነሳው የህወሓት ጁንታ፣ በስውር እና በአደባባይ የጫካ ልማዱን መሰረት አድርጎ ሲገድል መኖሩ አዲስ ባይሆንም፣ ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝቼ ነበር፡፡ የመገኘቴ ዓላማም የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 26 የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የዕውቅና ደብዳቤውን ለመስጠት የተያዘውን ቀጠሮ በማክበር ነበር፡፡
የሰላማዊ ሰልፍ እውቅናን በተመለከተ ኃላፊ የሆኑት አቶ ማርቆስ ፎርም እንዲሞላ አዘዙ፤ የተባለውን ፎርም ሞላን፤ ያን ጊዜ የአቶ ማርቆስ የቢሮ ስልክ አንቃጨለ፤ አነሱት ……ቀጭን ትዕዛዝ ከወዲያ ማዶ……………
‹‹የአንድነትን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ ዕውቅናው እንዳይሰጥ ይቆይ›› አቶ ማርቆስ ፊቱ ተለዋወጠ ‹‹ ይቅርታ አድርግልኝ የኔ ችግር አይደለም›› ሌላ ቃል ካፉ አልወጣም፡፡
«አልገባኝም ….ቀጠልኩ ….የአንድነት ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ እያልከኝ ነው ? »
መለሰ …..«እኔ ምን ላድርግ ? …..»
«የከለከለው ማነው የበላይ ኃላፊ ነው ? »
«አዎ» አጭር መልስ፡፡
ትቼው ወደ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊው አመራሁ፤ ስብሰባ ላይ ናቸው፡፡ ወደ ፓርቲ ጽ/ቤት ደውዬ ሁኔታውን አሳወኩ። የፓርቲው ፕሬዘዳንት ኢንጅነር ግዛቸውን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ፈጥነው ደረሱ፡፡ የአስተዳደሩ ስብሰባም ለሻይ እረፍት ተቋርጦ ኃላፊው ወደ ቢሯቸው ሲገቡ ተከታትለን ገባን፡፡ ላለማናገር ጥቂት አንገራገሩ ። የቢሯቸውን በር አንቀን አናግሩን በማለት ጸናን፡፡
‹‹ምንድነው ችግሩ የሰልፉ ጉዳይ ከሆነ ጨርሰናል፤ እውቅናውን ወሰዳችሁ አይደለም ? ›› አሉ።
ባጭሩ መልስ ተሰጣቸው ፤ «አልወሰድንም ። የአቶ ማርቆስ መልስ ተከልክሏል የሚል ነው፡፡ »
ጥያቄ አስከተልን ……«እርሰዎ መረጃ የለዎትም ? መንግስታዊ ኃላፊነቱ የርስዎ ነው፤ ማነው ከልካዩና ፈቃጁ ? »
መልስ የለም ። ጥቂት ዝም ብለው ‹‹የጠየቃችሁን ሚያዚያ 19 ለማድረግ ነበር፡፡ በዚያ ቀን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የጥበቃ እጥረት አለብኝ በማለት ስላመለከተ የእናንተ ሰልፍ ለሚያዚያ 26 እንዲደረግ ጠየቅናችሁ ። ተስማማን ከዚህ ውጪ የተደረገ ነገር ካለ በኔ በኩል መረጃ የለኝም። ማን እንደከለከለ አናውቅም››
« ስለዚህ ይህንን ከተማ ከንቲባው ካልሆነ ማን ነው የሚመራው? »
ከወዲያ ማዶ መልስ የለም……….ስልክ አነሱ እና አቶ ማርቆስን ወደ ቢሯቸው ጠሩ ። ሰውዬው መጡ ። ማጣሪያ ተጠየቁ። «መመሪያ ደርሶኛል» ሲሉ ለከንቲባው ጽ/ቤት ኃላፊ በኛው ፊት ተናገሩ፡፡ «መመሪያ ሰጪው ማነው?» ወደ አንዱ ቢሮ ዘው ብለን አንድ ሰው አናገርን ………..
‹‹እባካችሁ ይቅርባችሁ ደህንነቶቹ የሚውሉት እዚህ ግቢ ነው፡፡ አንድነቶች ከወጡ እርምጃ ይወሰድ ሲሉ ሰምቻለሁ›› አለን በማንሾካሾክ ድምጽ ………….
ጎበዝ ይሙት ሰነፍ ይኑር ቢሻው
አተላ መሸከም ይችላል ትከሻው………..
ፍርሃት ማነው ቢሉኝ ስሙን አላውቀውም
ሞትን በቁሜ እንጂ ሞቼ አልጠብቀውም፡፡
………………..ህወሓት ሊተኩስ ተዘጋጅቷል እኛም የነሱን ጥይት የሚሸከም ደረት …….እመነኝ ካልገደሉ አያቆሙንም፡፡፡

ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ "የኢህአዴግ ደጋፊም አባልም መሆን የምቸገረው ኢህአዴግ የሚያራምደው አብዮታዊ ዲሞክራሲ ለግለሰብ ነፃነት የሚሰጠው ቦታ ስለሌለ ወይም የይስሙላ ስለሆነ ነው፡፡ አሁንም አቋማችን መሆን ያለበት የእድገትና ትራንሰፎርሜሽን ዕቅድ የዜጎችን ነፃነት ቀምቶ የሚመጣ ከሆነ ባአፍንጫችን ይውጣ የሚል መሆን አለበት፡፡" ይሉናል።

ነፃነት የጎደለው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ 
ግርማ ሠይፉ ማሩ 
girmaseifu32@yahoo.com 
 
የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን በዝርዝር ተመልክቶ የገመገመ ተቃዋሚ ፓርቲ ከአንድነት በስተቀር ያለ 
አይመስለኝም፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች የዕቅዱን ግምገማ ውጤት ለህዝብ ለማድረስ ባለመቻሉ ግን ይህ የሚታወቅ 
ነገር አይደለም፡፡ ግምገማው የተከናወነው የተለያዩ ዘርፎችን ለሙያው ቅርበት ባላቸው ሰዎች በሚመሩት ሁኔታ 
ነው የተገመገመው፡፡ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን አንድ ክፍል ለመገምገም ሃላፊነት ከወሰዱት ሰዎች 
ውስጥ/አሁን ስም መጥቀስ አያስፈልግም/ ኢህአዴግ ይህን ዕቅድ ካሳካ ኢህአዴግ እሆናለሁ ማለታቸውን 
አሰታውሳለሁ፡፡ እኔ በግሌ ዕቅዱን እንደማያሳካ ሰጋቴን ባስቀምጥም እቅዱን ቢያሳኩትም ኢህአዴግ እንደማልሆን 
አውቃለሁ፡፡ እነዚህ ቁሳዊ ነገሮች የበዙበት ዕቅድ ነፃነቴን ለመውሰድ የተዘጋጀ እንደሆነ ይገባኛል፡፡ የኢህአዴግ 
ደጋፊም አባልም መሆን የምቸገረው ኢህአዴግ የሚያራምደው አብዮታዊ ዲሞክራሲ ለግለሰብ ነፃነት የሚሰጠው ቦታ ስለሌለ ወይም የይስሙላ ስለሆነ ነው፡፡ አሁንም አቋማችን መሆን ያለበት የእድገትና ትራንሰፎርሜሽን ዕቅድ የዜጎችን ነፃነት ቀምቶ የሚመጣ ከሆነ ባአፍንጫችን ይውጣ የሚል መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በተቃራኒው የሚቆም መብቱ ነው፡፡ በህዳሴው ግድብ ከሚገኝ መብራት ኢትቪን እየተመለከተ ነፃነቱን በእልሙ ማየት ይችላል፡፡ ወይም በህዳሴው ግድብ መነሻ በሚፈጠር ማነኛም የስራ ዕድል ተጠቃሚ ሆኖ ነፃነት ድሮ ቀረ ብሎ የሌሎች ሀገር ዲሞክራሲን ማወደስ ሲሻው መሳደብ መብቱ ነው፡፡ ነፃነት በነፃ አይገኝም ብቻ ሳይሆን ነፃነትን ለፈለጉት ቁሳዊ ጥቅም አሳልፎ መሸጥ የግለሰቦች ምርጫ ነው፡፡ ነፃነት የሚገኘው በ “ምርጫ” ነው፡፡ ነፃ ለመሆን በመፈለግና ለዚህ ፍላጎት የሚከፈለውን ዋጋ በመክፈል የሚገኝ ነው፡፡ 
 
እኛና ኢህአዴጎች የእድገትና ትራንሰፎርሜሽን ዕቅዱን በዕቅዱ ዘመን መጨረሻ ሰንገመግም እንዲሁም አቋም ስንይዝ በብርጭቆ ውስጥ እንደሚገኝ ውሃ “ግምሻ ሙሉ እና ግማሽ ጎዶሎ” በሚል ፍልስፍና መነፅር ኢህዴጎች ግማሽ ሙሉ እኛ ግማሽ ጎዶሎ እንደመረጥን ተደርጎ ቢወሰድ ልክም ተገቢም አይደለም፡፡ ኢህዴጎች ከአሁኑ እንደማይሆንላቸው ስላወቁ በዕቅድ ዘመኑ ከተቀመጡት “ወሳኝ ቁሳዊ ግቦች” ቢሆን ፈቀቅ ብለው፤ አሁን የደረሱበትን እና ወደፊት ያለውን “ተስፋ” በመመገብ ለቀጣይ ምርጫ እንደ ዋናኛ የምርጫ ግብዓት እየተዘጋጁ ነው፡፡ በቀጣይ ዓመት በዕቅድ የተቀመጡትን ግቦች ከማሳካት ይልቅ በዋነኝነት በፕሮፓጋንዳው ስለሚጠመዱ አሁን ከደረሱበት ብዙ ፈቀቅ እንደማይሉ ለመገመት አያስቸግርም፡፡ 
 
የኢህአዴግ ሰዎች በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ በእያንዳንዱ ዘርፍ የተጣለው ግብ በዋና ዋናዎቹ ግማሽ ለመደረስ እንደማይቻል አመላካች ነገሮች እንዳሉ ይረዳሉ፡፡ እንደዚያም ሆኖ ግን አጠቃላይ ግቡ ሊሳካ ይቻላል ብለው ማመን መርጠዋል፡፡ ግማሽ ሙሉ ፍልስፍናን እንደመስፈርት እንደንጠቀም የሚገፉንም ለዚህ ነው፡፡ ለዚህም መከራከሪያ ብለው ያስቀመጡት በመሰረታዊ ዕድገት አማራጭ ከአስራ አንድ በመቶ በላይ እናድጋለን ብለን ነበር አሰር በመቶ ከዚያም ትንሽ ዝቅ ያለ ቢሆንም ዋናው ዕቅዱ የተለጠጠ ስለነበር ጥሩ ነበር ብቻ ሳይሆን እጅግ በጣም ጥሩ የሚባል እንደሆነ ተደርጎ ስለሚነገረን መዘጋጀት ያለብን ይመስለኛል፡፡ ለምን? ቢባል መልሱ ባለ ብዙ ዘርፍ ነው፡፡ አንዱ በምክር ቤት ደረጃ ባሉ የኢህአዴግ አባላት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ አልተሳካም ተብሎ በሚመጣ ጣጣ ከሞቀ /አንፃራዊ ነው/ ወይም ከአዲስ አበባ ኑሮ ወደ ወረዳ መውረድ ሊያስከትል ይቻላል፡፡ ይህ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም እንዳሉት ወረዳ ወርዶ መስራት ቀላል አይደለም፡፡ ሌላው ደግሞ ይህ የተጠቀሰው ስጋት የብዙዎቹ ካድሬዎች ሊሆን ቢችልም ይህ ሰጋት የሌላቸው ጎምቶዎቹ ኢህዴጎች ግን የተንደላቀቀ የገዢነት ቦታ ላለማጣት የእድገትና ትራንስፎርሜሸን ዕቅድ በአብዛኛው ተሳክቶዋል በሚለው የመንግሰት ሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እኛንም እራሳቸውንም ለማሳመን መጣራቸው የማይቀር ነው፡፡ በኢህዴግ የሚዲያ አጠቃቀም ስትራቴጂ 
የተወሰኑ ሰዎች ሰለጉዳዩ የፈለገ ጥልቅ እውቀት ቢኖራቸው አጠቃላይ ህዝቡን በተለይም ለስልጣኝ መሰረቴ ነው የሚለው ድሃውን 
እስካታለለ ድረስ ስለ መረጃ ትክክለኝነት አይጨነቅም እና ለዚህ በሚደረግ ሽርጉድ እኛንም እውነት እስኪመስለን ድረስ ይህን እውሸት ልንሰማው መቻላችን በቅርብ ርቀት ያለ ሀቅ ነው፡፡ 
 
የዚህ ፅሁፍ መነሻ በቅርቡ በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ሶስተኛ ዓመት አፈፃፀም ግምገማ አሰመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሪፖርት ቀርቦ ነበር፡፡ ሪፖርቱን ተከትሎ የኢህአዴግ አባላት የሚሰጡት አስተያየት ሪፖርቱን ያነበቡት አይመስሉም፡፡ ከሪፖርቱ ይዘት ይልቅ ቀልባቸውን የሳበው የኢቲቪ ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡ ሪፖርቱ በግልፅ ዋና ዋና የተባሉትና ዕቅዱ በቀረበበት ወቅት እነዚህ ዕቅዶች አሁን ባለ የፋይናንስ እና የመፈፀም አቅም የሚታሰቡ አይደሉም በሚል ትችት ሲቀርብባቸው የነበሩትን በሙሉ ለማሳካት የማይቻሉ እንደሆኑ አሳይቶዋል፡፡ ይህ ደግሞ ሲቀርብ የነበረው ትችት ትክክለኛነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ የቀረበው ሪፖርት “በአጠቃላይ በመሰረተ ልማት ፕሮግራሞች አፈፃፀም ዙሪያ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ሁለንተናዊ አቅም ማነስ፤ የመሰረተ-ልማት ግንባታና ማማከር አግልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ተቋማዊ አቅም ማነስ እና የፋይናንስ እጥረት ቁልፍ ማነቆዎች ሆነው ታይተዋል” ይላል፡፡ ሲጀመር እኛም ያልነው ኢህአዴግ በሚመራት ሀገረ ኢትዮጵያ ከላይ የተጠቀሱት ዋና ግብዓቶች ማነቆ ስለሆኑ እንደዚህ ያለ የተለጠጠ ዕቅድ መሳካቱ ያጠራጥራል ነው እንጂ በዓለም ላይ በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ላይ የሰፈሩት ፕሮጀክቶ አይተገበሩም መተግበር የማይችሉ አስማት ናቸው አላልንም፡፡ አንባቢ ልብ እንዲልልኝ የምፈልገው በእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን መጨረሻ የሀገራችን እድገት 11.2 በመቶ አማካይ ይሆናል 
የተባልነው፤ የኢንዱስትሪ/ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከ20 በመቶ በላይ፤ የአስፋልት መንገድ ሳይጨምር የገጠር ቀበሌዎችን ከዋና መንገድ ጋር የሚያገናኙ ከ71 ሺ ኪሎ ሜትር ክረምት ከበጋ የሚያገለግሉ መንገዶች ግንባታ፤ የአዲስ አበባን ቀላል ባቡር ግንባታን ሳይጨምር 2395 ግርማ ሠይፉ ማሩ ኪሌ ሜትር የባቡር መስመር ግንባት፤157 ሺ ቤቶችን መገንባት፤ 10 ሺ ሜጋ ዋት የሚደርስ የኢነርጂ ልማት፤ በስኳር ልማት የሀገር ውስጥፍጆታን ሸፍኖ ከስድሰት መቶ ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሪ ማሰገባት፤ በማዳበሪያ ምርት ከፊል የሀገር ውስጥ ፍጆታን መሸፈን፤ወዘተ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ አሰማተኛውን የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ድርጅት የተሰጠውን ተግባር የተቀመጠለትን ግብ ትተን ማለት ነው፡፡ በግብርና ዘርፍ በሰፋፊ እርሻ የታቀዱትን ዝርዝር ግቦችንም ሳንረሳ ማለት ነው፡፡ 
 
እነዚህ ሁሉ በማነኛውም መመዘኛ በዕቅዱ ዓመት ማጠናቀቂያ የዕቅዱን ግማሻ ሊያሳኩ እንደማይችሉ ለመገመት ነብይ መሆን 
አይጠይቅም፡፡ ከላይ ከተዘረዘሩት ዋና ዋና በተለይም ኢቲቪ ለፕሮፓጋንዳ የሚጠቀምባቸውን እንደማሳያ ወስደን እንመልከት፡፡ የባቡር መስመር ዝርጋት ከተጣለለት ግብ 2395 ኪሎ ሜትር በዕቅድ ዘመን 239 ኪሎ ሜትር ወይም 10 ከመቶ ማሳካት አይቻልም፡፡ በኢነርጂ ዘርፍ የህዳሴው ግድብ ያማነጫል ተብሎ የሚጠበቀውን 750 ሜጋ ዋት እና ግልገል ጊቤ 3ን ጨምሮ አጠቃላይ የሀይል አቅርቦት የእቅዱን ግማሽ ማድረሽ ከባድ ነው፡፡ የማኑፋክቸሪንግ ሴክተሩ የተጣለወን ሃያ በመቶ እድገት ለማሳካት የሚያስችል የግል ሴክተር ተነሳሽነት አይታይም፤ ቢመጣም ማነቆ ብዙ ነው፡፡ የማዳበሪያ ፋብሪካ የብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ኮንትራቱን ለወዳጅ ዘመዶቹ ቆርሶ በመስጠት /sub-contracting ለሙስና የተጋለጠ አሰራር አለ እየተባለ አሜት ውስጥ ነው፡፡ በዚህ መስመር ምንም የሚታይ እንደሌለ ልማታዊው ኢቲቪ ምስክር ነው፡፡ በቤቶች ግንባታ በአዲስ አበባ ከ850 ሺ በላይ ቤት ፈላጊዎች ቢመዘገቡም በዕቅድ የያዙትን ያህል መስራት ሳይሆን ከተማውን ማፍረስ ነው የተያያዙት፡፡ እነዚህን ሁሉ ደምረን ስናያቸው የ11.2 በመቶ እድገት እንደማይመጣ እነርሱም እኛም ብናውቅ የፖለቲካ ቁጥር ሁለት አሃዝ እድገት ከ 10 በመቶ በላይ እድገት አሰመዝገበናል ይህም ከሰሃራ በታች ካሉ አገሮች ጋር ሲነፃፀር በእጥፍ ይበልጣል እንባላለን፡፡ እንዴት ነው ጎበዝ ይህ ነገር ልክ አይደለም ስንል ፀረ ልማት የሚል ቅፅል የያዘ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ይከፈታል፡፡ እንግዲህ ሁሉም ከዚህ አንፃር መዘጋጀት ያለበት ይመስለኛል፡፡ 
 
የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ሲጠናቀቅ ኢህአዴግ ቀጣይ የአስር ዓመት መሪ ዕቅድ እንደሚያቀርብ ፍንጭ የሚሰጡ ነገሮች እየታዩ ነው፡፡ አዲስ የተቋቋመው በአቶ መኮንን ማንያዘዋል ኮሚሽነርነት የሚመራው የዕቅድ ኮሚሽን ይህን ሃላፊነት ወስዶ እየሰራ ነው፡፡ ቀጣዩ እቅድ የአምስትም ይሁን የአስር አንድ ሀገር ከዚያም ያለፈ መሪ እቅድ እንዲኖራት ማድረግ ራዕይ ካለው መሪና ፓርቲ ይጠበቃል፡፡ በቀጣይ አስር ዓመትም ያለነፃነት ቁሳዊ ግቦችን አስቀምጦ ለመመራት ፍላጎት ያለውን ማነኛውንም ቡድን ግን እያንዳንዱ ዜጋ እንቢ ማለት ያለበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ጊዜው አሁን የሚሆንበት ገፊ ምክንያትም ኢህአዴግ አሳካለው ብሎ ያቀደውን ቁሳዊ እቅድ እንኳን ለማሳከት አቅም እንደሌለው አስመስክሮዋል፡፡ ቀጣዩን ዘመን ከቁሳዊ ግቦች በተጨማሪ ነፃነታችንን የማይገዳደር ዲሞክራሲያዊ ሰርዓት ለሚገነባ ቡድን እድል ለመስጠት መዘጋጀት ይኖርብናል፡፡ ኢህአዴግም ድርቅናውን ትቶ በቁሳዊ ዕቅድ ግማሽ ያደረሰውን ብርጭቆ ሳይሰብር ሌሎች የድርሻቸውን መወጣት የሚችሉበት እድል መኖሩን መቀበል ይኖርበታል፡፡ ነፃነት የራቀው የቁሳዊ እቅድ ጋጋታ መቀበል ያለመቀበል የነፃ ዜጎች ምርጫ እንጂ ፀረ ልማት መሆን ወይም የሀገር ልማት መጥላት አይደለም፡፡ 
 
ቸር ይግጠመን 

Friday, April 18, 2014

የአለም አቀፍ ፕረስ ተቇም (International Press Institute) አባላት ደቡብ አፍሪካ ላይ ባካሔዱት 63ኛ አመታዊ መደበኛ ስብሰባ ላይ የኢትዮጲያን መንግስት የጸረ ሽብር አዋጅን በመጠቀም ጋዜጠኞችን ማሰሩን እንዲያቆም ጠየቁ።

Ethiopia: Stop Arresting Journalists Under Anti-Terror Laws, Says IPI

እንደ አዲስ አድማስ ዘገባ "የአማራ ተወላጆች ናችሁ የተባሉ በሱሉልታ ከተማ ተደበደቡ" ከቅርብ ጊዜ ወዲ በተላያዩ ብሔረሰቦች መካከል እየተፈተረ ያለው ግጭት የወያኔ "ከፋፍለህ ግዛ" ውጤት መሆኑ ይታወቃል።

አዲስ አድማስ – በሱሉልታ ከተማ የአማራ ተወላጆች ናችሁ የተባሉ ተደበደቡ(ናፍቆት ዮሴፍ)


ሶስት ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው በአዲስ አበባ የተለያዩ ሆስፒታሎች ገብተዋል
“ረብሻውን ያነሱት ህዝብን የማይወክሉ ወሮበሎች ናቸው” የከተማው ኮሙዩኒኬሽን
“ባህርዳር በተካሄደው የስፖርት ውድድር ላይ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ አድልዎ ተፈጽሟል” በማለት የተቧደኑ ወጣቶች፣ ባለፈው ሐሙስ የሱሉልታ ከተማ ነዋሪ የሆኑ በርካታ የአማራ ተወላጆች ላይ ድብደባ ፈፀሙ፡፡
በድብደባ በርካታ ሰዎች ከመጐዳታቸውም በተጨማሪ፤ ቤት ንብረት ላይም ጥፋት እንደደረሰ የተናገሩት ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች ጉዳዩን ሕገወጥ ነው ሲሉ አውግዘውታል፡፡ የከተማዋ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ፤ የስፖርት ውድድርን ሰበብ በማድረግ ረብሻ የቀሰቀሱ ሰዎች ህዝብን የማይወክሉ ወሮበሎች ናቸው ብለዋል፡፡
ረብሻውን ቀስቅሰዋል ተብለው ከተጠረጠሩት ውስጥ አራቱን በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለም ገልፀዋል ሃላፊው፡፡ “የቤቴ በርና መስኮት እንዳልነበር ሆኗል፤ አጥር ተገነጣጥሏል፤ መስኮቶች ዱቄት ሆነዋል” ያሉት አንድ የከተማዋ የረጅም ጊዜ ነዋሪ፤ ከ30 በላይ ቤቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል፡፡ የስድስት ልጆች እናት እንደሆኑ የገለፁልን ሌላዋ ነዋሪ፤ በቤታቸውና በንብረታቸው ላይ አደጋ መድረሱን ጠቅሰው፤ እንደሌሎች ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ባያጋጥማቸውም በእጃቸው ላይ በደረሰባቸው ጉዳት በከተማዋ አንድ ክሊኒክ ህክምና እንደተደረገላቸው ተናግረዋል፡፡
“ይህ ህዝቡ በሰላም አብሮ እንዳይኖርና እንዳይግባባ ሆን ተብሎ የሚጫር የነገር እሳት ነው” ያሉት የ56 አመት አዛውንት በበኩላቸው፤ መንግስት መፍትሔ ከላበጀለት በቀር በአሁኑ ወቅት ከየአቅጣጫው የምንሰማው በዘር ተቧድኖ ግጭት የመፍጠር ጉዳይ አስጊ ነው ብለዋል፡፡
የከተማው አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ መሳይ ከበደ፤ ከከተማ አስተዳደር በደረሳቸው ሪፖርት ተዘዋውረው እንደተመለከቱ ገልፀው፣ የተወራውን ያህል ባይሆንም የስምንት ቤቶች የበርና የመስኮት መስታወቶች ተሰባብረዋል፤ የቆርቆሮ አጥሮች ተገነጣጥለዋል ብለዋል፡፡ ሰዎች አራት እንደተጐዱና የሶስቱ ሰዎች ጉዳት ከፍተኛ ስለሆነ በአዲስ አበባ የተለያዩ ሆስፒታሎች ውስጥ በክህምና ላይ መሆናቸውን አቶ መሳይ ጠቅሰው፤ አንዲት እናት በእጃቸው ላይ መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸው በከተማው ጤና ጣቢያ ታክመው ተመልሰዋል ብለዋል፡፡
“የረብሻው መንስኤ በቅርቡ ባህርዳር የተካሄደው የመላው ኢትዮጵያ ጫዋታዎች ውድድር ላይ በኦሮሞ ተወላጆች ላይ አድልዎና ተፅእኖ ተደርጓል የሚል ሰበብ ነው” ብለዋል አቶ መሳይ፡፡
“በረብሻው ዙሪያ ህዝቡንና የከተማ ነዋሪውን በመሰብሰብ ረብሻውን ያስነሱት ሰዎች ህዝብን የማይወክሉ እና ህዝብን ለማጋጨት ፍላጎት ያላቸው የተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች መሆናቸውን ተወያተናል” ያሉት የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊው፣ ህዝቡ እንዲህ ዓይነት ቡድኖችም ሆኑ ግለሰቦችን አሳልፎ እንዲሰጥ ተግባብተናል ብለዋል፡፡ ረብሻው ወዲያውኑ በፖሊሶችና ከጫንጮ በመጡ የፀጥታ ኃይሎች መቆሙን ተናግረዋል – ሃላፊው፡፡

Thursday, April 17, 2014

ከግንቦት 7 ንቅናቄ ለብዙሃኑ የመከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊት የተላለፈ ጥሪ። "እስከመቼ ለህወሓትና ጥቂት አጎብዳጅ መኮንኖች ባርነት ትገዛለህ? ይህ ውርደት የሚያበቃው መቼ ነው? የታጠከው መሣሪያ የአገርህና የራስህ ክብር ማስጠበቂያ፤ ነፃነትን መጎናፀፊያ የምታደርገው መቼ ነው?"

ይድረስ ለብዙሃኑ የሠራዊቱ አባል ወገናችን!!

የመከላከያ ሚኒስትር በተሰኘው የውሸት ሥልጣን ላይ የተቀመጠው አድርባይ ሲራጅ ፈርጌሳ ለይስሙላው ምክር ቤት ባቀረበው ሪፓርት፣ “የመከላከያ ሚኒስትር የብሔር ተዋጽዖ የተመጣጠነ” እንደሆነ ገለፀ። እንደ ሰውየው ሪፓርት ከሆነ የመከላከያ ሠራዊቱ 29.46 በመቶ አማራ፣ 25.05 በመቶው ከደቡብ ብሔሮች የተውጣጣ፣ 24.45 በመቶ ኦሮሞ፣ 17.47 በመቶው ትግራይ እና የተቀሩት ክልሎች ድርሻ 4.17 በመቶ ነው። መረጃው የተቀናበረው በክልል ቢሆንም የቀረበው ግን በዘር ነው። “ተመጣጠነ” የተባለውም የክልሎች ተዋጽዖ ሳይሆን የዘር ተዋጽዖ ነው። ሠራዊቱን እንዲህ በዘር ሸንሽንኖ የስታትስቲክስ ጨዋታ መጫወት አሳዛኝም አሳሳቢም ነገር ነው። የሆነ ሆኖ ይህ መረጃ፣ መረጃ ነው ተብሎ ለሕዝብ ቀርቧል።
ይህንን መረጃ የሰማ ማሰብ የሚችል አዕምሮ ያለው ሰው የሚጠይቀው የመጀመሪያ ጥያቄ “የሠራዊቱ ስብጥር በተገለፀበት ዓይነት የመኮንኖቹም ስብጥር ለምን አልተገለፀም?” የሚል ነው። ይህ ጥያቄ በአስተዋይ ሰው አዕምሮ ውስጥ በተነሳነበት ፍጥነት ምላሽ ያገኛል፤ ምክንያቱም ምላሹ እዚያው እቁጥሮቹ ውስጥ አለ። የመኮንኖቹ ስብጥር ያልተነገረበት ምክንያት አብዛኞቹ መኮንኖች በ17.47 በመቶው በመሆናቸው ነው። ወደዚህ መምደሚያ የሚደርሰው አሳቢው ስለፈለገው ሳይሆን የመረጃው አቀራረብ አመክኖ (ሎጂክ) ወደዚያ ስለሚገፋ ነው። በዚህም ምክንያት በሲራጅ ፈርጌሳ አንባቢነት የቀረበው የህወሓት ሪፓርት በገዛ ራሱ ላይ ነው የተኮሰውም።
እኛ እንደ ሲራጅ ፈርጌሳ የዘር ስታትስቲክስ ውስጥ አንገባም፤ መልዕክታችን ለተገፋውና እየተበደለ ላለው ለመላው የሠራዊቱ አባል ነው።
ይድረስ ሹመትና ኃላፊነት ተነፈገህ፤ የጥቂቶቹን ሀብትና ዝና ጠባቂ እንድትሆን ለተፈረደብህ ወገናችን!!! እስከመቼ ለህወሓትና ጥቂት አጎብዳጅ መኮንኖች ባርነት ትገዛለህ? ይህ ውርደትህ የሚያበቃው መቼ ነው? የታጠቀው መሣሪያ የአገርህና የራስህ ክብር ማስጠበቂያ፤ ነፃነትህን መጎናፀፊያ የምታደርገው መቼ ነው? ለመሆኑ ለመኮንንነት የሚያበቃ ጭንቅላት፣ ልምድ ወይም እውቀት ከፓርቲ አባልነት ነው የሚገኘው? ህወሓቶችና አጋሮቻቸው በሠራዊቱ ያሉትን ቁልፍ ኃላፊነቶችን ሁሉ ጠቅልለው ይዘው “ጀሌዎቻችን እንዲሆኑ ፈቅደንላቸዋል” የሚል ሪፓርት የሚያቀርቡት ምንኛ ቢንቁን ነው? ይህንን ውርደት ኢትዮጵያዊው ወኔህ እንዴት ይቀበለዋል?
ኢትዮጵያዊው ወታደር ከሌላው ኢትዮጵያዊ በባሰ በአምባገነንና ዘረኛ አለቆቹ እየተዋረደ እንደሆነ በገሃድ የሚታይ ጉዳይ ነው። የህወሓት አባላት ቁልፍ የስልጣን ቦታዎችን ይዘው ጦር ሠራዊቱን እንደ ፓርቲ መዋቅር ሲመሩት ማየት የሠራዊቱን አባላት ብቻ ሳይሆን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚያንገበግብ ጉዳይ ነው። ሠራዊቱ አገርና ሕዝብን ሊጠብቅበት ይገባ የነገረው መሣሪያ በንጹሃን ዜጎች ላይ እንዲያነሳ፤ ሰላማዊ ሰዎችን እንዲደበድብ፣ እንዲረግጥና እንዲገድል የሚያዙት እነዚህ የህወሓትና ጥቂት አጎብዳጅ አለቆቹ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቃል። ሆኖም የኢትዮጵያ ወታደር የታዘዘው ሁሉ የሚፈጽም ባርያ አይደለምና በእነዚህ ጥቂት ዘረኛ አለቆችህ ላይ እንዲነሳ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይጠይቃል።
ውድ የኢትዮጵያ ወታደር ሆይ!!! “ዘረኛነት በቃኝ” በል። ለነፃነት፤ ለእኩልነት፤ ለአገር ክብር በሚታገሉ ወገኖችህ ላይ ክንድህን አታንሳ። የጥቂት ዘረኞችን ሥልጣን በማራዘም ከሚመካብክ የኢትዮጵያ ድሃ ሕዝብ ጋር ዘላቂ ቂም ውስጥ አትግባ። በትእቢት “ሁልሽንም ረግጠን እንገዛለን” ብለው የሚፎክሩት አንተን ከወገንህ ጋር ደም በማቃባት ነውና “እምቢ!” በላቸው። ለዘረኞች ስልጣን ብለህ አትሙት! እንዲያውም ለገዛ ራስህ ክብር፣ ለቤተሰቦችህና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነፃነት ግንባር ቀደም አርበኛ ሁን።
ከላይ የተባለው ለፓሊስ አባላትም ይሠራል። በህወሓትና ህወሓት በየቦታው በፈጠራቸው ጀሌዎች የሚመራ በመሆኑ ከሕዝብ ፍላጎት በተፃፃሪ የቆመ ይምሰል እንጂ የኢትዮጵያ ፓሊስ የሕዝብ ወገን እንደሆነ በተለያዩ አጋጣሚዎች የታየ ጉዳይ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍትህ እጦት የሚሰቃየውን ያህል ብዙሃኑ ፓሊስ በፍትህ እጦት እየተሰቃየ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ የኑሮ ጫና እንዳዳከመው ሁሉ የኢትዮጵያ ፓሊስም ኑሮ ከብዶታል። እንደሌላው ሰው ሁሉ ፓሊስንም ዘረኝነት አስመርሮታል። ብዙሃኑ ፓሊስ አቅሙን በጥቂት አምባገነን አለቆቹ ላይ የሚፈትሽበት ጊዜ ደርሷል።
የስለላ ተቋማቱ ጉዳይ ለየት ይላል። “ደህንነት” ተብሎ በሚሞካሸው የጆሮጠቢዎች ስብስብ በሆነው መሥሪያቤት እና በኤክትሮኒክስ ብርበራ የተሠማሩ “ባለሙያ ጆሮ ጠቢዎች” ውስጥ ህወሓት በአለቃነትም በምንዝርነትም አብዛኛውን ቦታ ይዟል። ሆኖም እዚህም የሕዝብ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃሉ። በእነዚህ ቦታዎች ያላችሁ የሕዝብ ወገኖች ሲቻል በገሃድ ሳይቻል በሚስጥር ተቋማቱን የማዳከም ሥራችዎችን መሥራት የህሊናና የዜግነት ግዴታችሁ ነው። ከእናንተ ብዙ፤ እጅግ ብዙ ይጠበቃል። የምታሾልኳት ትንሿ መረጃ የብዙዎችን ሕይወት ልትታደግ ትችላለች፡
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት የጦር፣ የፓሊስና የስለላ መዋቅሮች ውስጥ የሕዝብ ወገኖች እንዳሉ ያውቃል። እነዚህ ወገኖቻችን እንደሌላው ሕዝብ ሁሉ – አንዳንዴም ከሌላው በባሰ ሁኔታ – በፍትህ እጦት፣ በኑሮ መክበድና በዘረኝነት እየተሰቃዩ መሆናቸው ያውቃል። እነዚህ ወገኖቻችን ጥለው እንዲወጡ፤ ይህ ካልተቻለም ከውስጥ ሆነው የወያኔን የጦር፣ የፓሊስና የስለላ መዋቅሮች እንዲያፈራርሱ ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የወያኔ መንግስት ግብረሰዶማዊነትን ለመቃወም ሊደረግ የታቀደውን ሰላማዊ ሰልፍ ሰረዘ።

Planned anti-gay rally in Ethiopia is cancelled

Wednesday, April 16, 2014

መቇጫ ያልተግኘለት እና ደብዛው ጠፍቶ የቆየው የማሌዢያው አውሮፕላን መጠለፉን እና በአሁኑ ሰዓት ካንዳሃር በሚባለው የአፍጋኒስታን ክፍለ ሃገር ውስጥ "ሂትች" በሚባል የአሸባሪዎች ቡድን ተጠልፎ እንደሚገኝ የሩስያ ጋዜጣ ዘገበ።

Russian Newspaper Says Missing Malaysian Plane In Afghanistan And Hostages Divided Into 7 Groups

Posted on 4/16/2014 by 



A report is saying that missing Malaysia Airlines Flight MH 370 is located in Kandahar Province, and a terrorist named “Hitch” is behind the disappearance.

6
A Russian newspaper, Moskovsky Komsomolets, said that the plane was hijacked and taken to Afghanistan and the passengers are now being held captive.
“Flight MH370 Malaysia Airlines missing on March 8 with 239 passengers was hijacked,” the Russian paper says. ”Pilots are not guilty; the plane was hijacked by unknown terrorists. We know that the name of the terrorist who gave instructions to pilots is ‘Hitch.’ The plane is in Afghanistan not far from Kandahar near the border with Pakistan.”
The report said that the passengers were divided into seven different groups and are living in huts with little food.
However, the Moskovsky Komsomolets report didn’t offer much in terms of sources–including names or even the identity of the intelligence agency it got its information from.
And Australian search teams are focusing on scouring the southern Indian Ocean for the plane and its black boxes. A submarine is now being used to look for the wreckage.
The alleged hijacking has not been confirmed by Malaysia. The Russian news report also said the terrorists are bargaining with Chinese and Malaysian officials, which also wasn’t confirmed by either country.
There were reports more than a month ago from The Independent newspaper–before Malaysian officials announced that the flew over the Indian Ocean and crashed–saying officials were exploring the possibility the plane may have been hijacked to Pakistan or Afghanistan.
The Independent said at the time: “The missing Malaysian airlines flight MH370 may have been deliberately flown under the radar to Taliban-controlled bases on the border of Afghanistan, it has emerged, as authorities said that the final message sent from the cockpit came after one of the jet’s communications systems had already been switched off.”
The Pakistani Taliban has previously denied hijacking the plane.
A robotic submarine looking for the lost Malaysian jet continued its second seabed search on Wednesday as up to 14 planes were to take to the skies for some of the final sweeps of the Indian Ocean for floating debris from the ill-fated airliner.
The U.S. Navy’s Bluefin 21 submarine began its second 20-hour underwater mission on Tuesday after cutting short its first because the ocean waters where it was sent were too deep, officials said.
The unmanned sub is programmed to hover 30 meters (100 feet) above the seabed, but it started searching atop a patch that was deeper than the sub’s maximum operating depth of 4,500 meters (15,000 feet), the search coordination center and the U.S. Navy said.
A built-in safety feature returned the Bluefin to the surface and it was not damaged, they said.
The data collected by the sub was later analyzed and no sign of the missing plane was found, the U.S. Navy said.
Crews shifted the search zone away from the deepest water before sending the Bluefin back for Tuesday’s mission, the U.S. Navy said.
The search coordination center said 11 military planes and three civilian planes would search a 55,000-square-kilometer (21,000-square-mile) expanse of ocean on Wednesday centered 2,000 kilometers (1,300 miles) northwest of the Australian west coast city of Perth. Eleven ships would also join the search.
The Associated Press contributed to this report.

በህዳሴው ግድብ አቅራቢያ የታጠቁ ሰዎች የህዝብ ማመላለቫ አውቶቢስ ላይ በከፈቱት ቶክስ 9 ሰዎች ሲገደሉ 7 ደሞ ቆስለዋል። አሶሺየትድ ፕረስ ነው የዘገበው።

Gunmen Kill 9 on Bus in Ethiopia Near Dam Project

Monday, April 14, 2014

በአሳፋሪ ሁኔት ላይ የሚገኘው የኢትዮጲያ የከፍተኛ የትምህርት ተቇማት እና ወያኔ እንዴት አድርጎ እንዳሽመደመዳቸው ግንዛቤ ለማግኘት የሚከተለውን ጽሁፍ ይመልከቱ።

The Disgraceful State of Higher Education in Ethiopia: How TPLF/EPRDF Killed Higher Learning

by admin
by Alem Mamo
TPLF/EPRDF’s major bragging source over the last number of years has been its ‘achievements’ in the education sector, particularly in university education. The ruling group constantly brandishes its statics about the ‘expansion’ of higher learning in Ethiopia. What is not included in the fraudulent statistics is the obliteration of quality and depth of teaching and learning in these so-called ‘universities.’  As we have seen in most of the TPLF/EPRDF failed and corrupt policies the establishment of these so called ‘universities’ is nothing more than a construction contract to its own business conglomerates and university administration appointment to its loyal cadres.

A university is more than a building. A university in its true form requires several contextual, philosophical, and logistical grounds to fully carry out its historical and traditional role as a place of higher learning.
The higher learning landscape in Ethiopia under TPLF/EPRDF suffers from four acute problems. First, there is a chronic lack of academic freedom and autonomy, which is an essential component for any university to discharge its responsibilities. Second, there is an absence of qualified and competent instructor and mentors. Third is the almost non-existent nature of 21st century tools, such Internet communication, and finally there is the occupation and control of higher learning institutions by uneducated TPLF/EPRDF cadres. These key factors, coupled with the overall social, economic, and political problems, continue to plague the country’s higher learning landscape equating to a level similar to the mass wedding ceremonies orchestrated by a religious group lead by a self-proclaimed messiah, such as Reverend Sun Myung Moon[1]
In fact the assault on higher learning began in 1993 when TPLF/EPRDF fired 42 seasoned academics from Addis Ababa University and replaced them with its loyal cadres.[2] Ever since then the ruling group has continued to destroy higher learning under the guise of ‘expanding’ education. Universities and educational institutions in general are places where students are taught how to think, instead of what to think. Furthermore, universities are places in which curious learners are provided with the tools and the support to conduct research that has practical values in the social, economic, and political life of the society. Instead, the regime has built political re-education camps[3]where political cadres have the final word on the academic, social, and administrative life of an institution.
Indeed merit and qualification has never been TPLF/EPRDF’s s strong suit. Starting from senior cabinet positions to all the way to the lowest level of the administrative body they have appointed their cadres to run the country, and, quite frankly, the regime is not going to treat universities in any different way.
‘Massification’ of higher learning in Ethiopia, preferring quantity of graduates to quality, has reached a critical stage, and it is becoming very problematic to use the term ‘university’ to describe these diploma mills. In TPLF/EPRDF’s Ethiopia every institution is forced to be subordinate to the twisted ideology of the regime. The first and foremost pillar of a university anywhere in the world is autonomy and academic freedom. These two elements are the oxygen of a free learning and teaching environment. Contrary to this the ruling group maintains full control over these institutions depriving them the oxygen of freedom they desperately need to breath and function freely.
Maintaining its well-established destructive role TPLF/EPRDF is moulding higher learning institutions in its own image, and the image is not pretty. Infused with ugly and hate filled propaganda, the image of these so-called universities looks like this: (a) all of these institutions must maintain perceived or real ethnic polarization and tension;
(b) These institution must serve to promote TPLF/EPRDF’s divisive agenda; (c) all ‘university’ senior management, including presidents, must be members of the TPLF or TPLF manufactured political organizations; (d) critical thinking and questioning the prevailing orthodoxy equals terrorism; and (e) university campus informants are part and parcel of the security and surveillance structure of the regime.
The overall decline of the quality of higher learning in Ethiopia is evident in the African and world university rankings.  Currently, according to the African Economist University Rankings, only one university out of 35 so-called universities in Ethiopia appears on the ranking chart.[4] The rest are nowhere to be seen on any of university rankings.
We have come to be accustomed with TPLF/EPRDF lies, such us tyranny is democracy, repression is freedom, concentration of wealth in the hands of its inner circle is economic growth and development. The most tragic one is their political re-education camp ‘universities’.
Finally, one cannot understand the sad state of higher education in Ethiopia without understanding TPLF/EPRDF’s distractive political and economic agenda. Ultimately, these daunting challenges are intertwined and interconnected, therefore they only can find a solution when the fundamentals of the governance parameters are addressed.  Freedom, justice, and democratic accountability are the only solution. In the meantime, those who are enrolled in these institutions should continue to demand better quality as part of their struggle for a free, just, and democratic society.

አንድ ግለሰብ አማራ በመሆናቸው ብቻ በገጀራ ዘግናኝ ግድያ ተፈጸመባቸው። የተገደሉት አቶ ጌጡ ክብረት ይባላሉ የሰባት ልጆች አባት ናቸው ከተገደሉ በሁዋላ አይናቸውን አውጥተዋቸዋል። ሌላኛው አዛውንት እንደተናገሩት ደግሞ ብልታቸውን ሸንሽነዋቸዋል። ጎበዝ ኢትዮጲያችን ወዴት እየሔደች ነው? ወያኔ አሁኑኑ በቃህ ካልተባለ የሃገራችን እና የዜጎቿ ስቃይ ይቀጥላል።

ይህንን ምን እንበለው ? ኢህአዴግ ያለው ነገር የለም

አማርኛ ተናጋሪው ይህንን ምን እንበለው ? ኢህአዴግ ያለው ነገር የለም
አማርኛ ተናጋሪው በገጀራ ዘግናኝ ግድያ ተፈጸመባቸው

"መኖሬን ጠላሁት። ራሴን እንዳልገድል ወንጀል ነው። ሰው እንዳልገድል ወንጀል ነው" በሚል ግራ መጋባት አንድ አዛውንት ይናገራሉ። ተበዳዮች ከእርሻ ስራ በሁዋላ የሚይዙትን በትር ፖሊስ ሰበሰበ። ከዚያም እገበያ ቦታ ላይ ገጀራና ጦር የያዙ ጎረምሶች እየጮሁ ጥቃት መፈጸም ጀመሩ። 16 ሰዎች፣ 26 ናቸው የሚሉ አሉ ጉዳት ደረሰባቸው። አንደ ኢ ሰው ተገደሉ።

ይህ ዜና የተወሰደው ተበዳዬች ራሳቸው ባንደበታቸው ሲናገሩ ከሚታዩበት ቪዲዮ ነው። የተገደሉት አቶ ጌጡ ክብረት ይባላሉ። የሰባት ልጆች አባት ናቸው። የተገደሉት በገጀራ ነው። ከተገደሉ በሁዋላ አይናቸውን አውጥተዋቸዋል። አንደኛው ተናጋሪ አዛውንት እንደተናገሩት ደግሞ "ብልታቸውን ሸንሽነዋቸዋል"


ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ለህክምና ሲሄዱ " ሂድና አገርህ ታከም። ይህ የእኛ ሃኪም ቤት ነው" እንደተባሉ ምስክሮቹ ይናገራሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው በምዕራብ ሸዋ ዞን ደኖ ወረዳ በሶስት ቀበሌ ገበሬ ማህበራት በሚኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ ነው።

ሰዎቹ እንደገለጹት ከጎንደር ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ነው ወደ ስፍራው የገቡት። በህጋዊ ማመልከቻና በህጋዊ የአስተዳደር አካላት ውሳኔ ቀደም ሲል የዝንጀሮ መንጋ የሚኖርበትን ስፋራ እንዳለሙ ይናገራሉ። በዚህም ላይ ህጋዊ ግብር የሚከፍሉ ናቸው። አንድ እንድሜያቸው የገፋ ተናጋሪ በቪዲዮው ላይ እንደተናገሩት " አስተዳደሩ ቻፓ መቶ" አስረክቧቸዋል።


ከሃያ ዓመታት በሁዋላ አሁን " አማርኛ ተናጋሪ ናችሁ። መሬቱን ለቃችሁ ውጡ" የተባሉት ሰዎች ለፌደራል ባለስልጣናት አቤቱታ ማቅረባቸው ይበልጥ ጉዳት አስከትሎባቸዋል። " እስኪ ምን ታመጣለህ" በሚል ያካባቢው አስተዳደር አካላት ቀልደውባቸዋል። ከሁሉም በላይ ግን ላለፉት ሃያ ዓመታት አብረዋቸው የኖሩ ሰዎች ዛሬ እንዴት ጨክነው ገጀራ አነሱ? የሚለው ጉዳይ ስጋት የሚጭር ሆኗል። በተለይም የፍትህ አካላትና ራሱ ኢህአዴግ፣ ብአዴን ሰው በገጀራ ሲገደል ዝም ማለታቸው ድርጊቱን አሳዛኝ ያደርገዋል።


በተለያዩ ክልሎች የተለያዩ ብሔረሰብ ተወላጆች አሉ። ተስማምተውና ተከባብረው ኖረዋል። አሁንም እየኖሩ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ከጥንት ጀምሮ ተዋልደው፣ ወልደውና ከብደው የኖሩ አማሮች ቁጥር ቀላል አይደለም። ኢህአዴግ አገር መግዛት ከጀመረ በሁዋላ ኦሮሚያ ላይ በኢንቨስትመንት ስም ሰፋፊ መሬትና የማዕድን ቦታ የያዙ አሉ። ህዝብ አነዚህ ኦሮሚያን እያለቡ ያሉትን ጠንቅቆ ያውቃቸዋል። በተለይም ንጹህ ህሊና ያላቸው ጉዳዩን ከነስሌቱ ይረዱታል። ከነዚህ "ባለጊዜዎች" ዝም ተብለው ምስኪ ጭሮ አዳሪዎች ላይ እንዲህ ያለው ተግባር መፈጸሙ ውሎ አድሮ ወዴት የሚያሰኝ ይሆናል። ነገም በስፋት በተለያዩ ስፋራዎች ድርጊቱ ስላለመቀጠሉ ዋስትና የለም። በሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ላይ።


እነዚህ ከጎንደር እንደመጡና ላለፉት 20 ዓመታት በስፍራው ላይ በህጋዊነት የሰፈሩት ወገኖች እነሱ ካሉት ውጪ ቦታው ላይ መኖር የማይችሉበት ህጋዊ አግባብ ካለ፣ ህጋዊ ጥፋት ወይም የመረጃ ችግር ካለባቸው በህግ ከሶና አስወስኖ አስፈላጊውን ውሳኔ ማሳለፍ ይቻላል። ህግና ስርዓት ባለበት አገር በትር በመንጠቅ ምስኪኖቸን በገጀራ ማስደብደብና ማስገደል ዘግናኝ ነው። ሰዎቹ እንዳሉት ሶስት ገበሬ ማህበር የሚሆኑ ናቸው። አንድ ገበሬ ማህበር ውስጥ ባማካይ 600 አባወራ አለ። በሶስት ሲባዛ የአባወራዎቹ ቁጥር ከፍተኛ ይሆናል። አሁንም እንሱ እንደገለጹት እያንዳዳቸው ባማካይ ስድስትና ሰባት ቤተሰብ አላቸው። እናም ጉዳዩ በቀላል የሚታይ አይሆንም።

“ አማራ በሚለው ደማችንና አጥንታችን አትውቀሱን" አልናቸው በማለት ሰዎቹ እንደገለጹት፣ ጥቃቱ የሚደርስባቸው በዘር ነው። ይህ ደግሞ ኢህአዴግ በተለይም ህወሃት የተከለው አጀንዳ ነው። ህወሃት በፕሮግራም ደረጃ አማራን የማትፋት እቅድ ይዞ ሲታገል የኖረ፣ አሁን ደግሞ ብአዴን የሚባል ላንቲካ/ ሲምቦል ድርጅት አስቀምጦ ይህንኑ የበታችነት ስጋቱ የፈጠረበትን ስሜት እያስተገበረ ነው። ብአዴን ውስጥ ያሉ ወገኖች ግን እስከመቼ በዚህ ይቀጥላሉ?
- ቪዲዮውን ከዚህ በታች አድምጡት

አማርኛ ተናጋሪው በገጀራ ዘግናኝ ግድያ ተፈጸመባቸው

"መኖሬን ጠላሁት። ራሴን እንዳልገድል ወንጀል ነው። ሰው እንዳልገድል ወንጀል ነው" በሚል ግራ መጋባት አንድ አዛውንት ይናገራሉ። ተበዳዮች ከእርሻ ስራ በሁዋላ የሚይዙትን በትር ፖሊስ ሰበሰበ። ከዚያም እገበያ ቦታ ላይ ገጀራና ጦር የያዙ ጎረምሶች እየጮሁ ጥቃት መፈጸም ጀመሩ። 16 ሰዎች፣ 26 ናቸው የሚሉ አሉ ጉዳት ደረሰባቸው። አንደ ኢ ሰው ተገደሉ።

ይህ ዜና የተወሰደው ተበዳዬች ራሳቸው ባንደበታቸው ሲናገሩ ከሚታዩበት ቪዲዮ ነው። የተገደሉት አቶ ጌጡ ክብረት ይባላሉ። የሰባት ልጆች አባት ናቸው። የተገደሉት በገጀራ ነው። ከተገደሉ በሁዋላ አይናቸውን አውጥተዋቸዋል። አንደኛው ተናጋሪ አዛውንት እንደተናገሩት ደግሞ "ብልታቸውን ሸንሽነዋቸዋል"


ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ለህክምና ሲሄዱ " ሂድና አገርህ ታከም። ይህ የእኛ ሃኪም ቤት ነው" እንደተባሉ ምስክሮቹ ይናገራሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው በምዕራብ ሸዋ ዞን ደኖ ወረዳ በሶስት ቀበሌ ገበሬ ማህበራት በሚኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ ነው።

ሰዎቹ እንደገለጹት ከጎንደር ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ነው ወደ ስፍራው የገቡት። በህጋዊ ማመልከቻና በህጋዊ የአስተዳደር አካላት ውሳኔ ቀደም ሲል የዝንጀሮ መንጋ የሚኖርበትን ስፋራ እንዳለሙ ይናገራሉ። በዚህም ላይ ህጋዊ ግብር የሚከፍሉ ናቸው። አንድ እንድሜያቸው የገፋ ተናጋሪ በቪዲዮው ላይ እንደተናገሩት " አስተዳደሩ ቻፓ መቶ" አስረክቧቸዋል።


ከሃያ ዓመታት በሁዋላ አሁን " አማርኛ ተናጋሪ ናችሁ። መሬቱን ለቃችሁ ውጡ" የተባሉት ሰዎች ለፌደራል ባለስልጣናት አቤቱታ ማቅረባቸው ይበልጥ ጉዳት አስከትሎባቸዋል። " እስኪ ምን ታመጣለህ" በሚል ያካባቢው አስተዳደር አካላት ቀልደውባቸዋል። ከሁሉም በላይ ግን ላለፉት ሃያ ዓመታት አብረዋቸው የኖሩ ሰዎች ዛሬ እንዴት ጨክነው ገጀራ አነሱ? የሚለው ጉዳይ ስጋት የሚጭር ሆኗል። በተለይም የፍትህ አካላትና ራሱ ኢህአዴግ፣ ብአዴን ሰው በገጀራ ሲገደል ዝም ማለታቸው ድርጊቱን አሳዛኝ ያደርገዋል።


በተለያዩ ክልሎች የተለያዩ ብሔረሰብ ተወላጆች አሉ። ተስማምተውና ተከባብረው ኖረዋል። አሁንም እየኖሩ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ከጥንት ጀምሮ ተዋልደው፣ ወልደውና ከብደው የኖሩ አማሮች ቁጥር ቀላል አይደለም። ኢህአዴግ አገር መግዛት ከጀመረ በሁዋላ ኦሮሚያ ላይ በኢንቨስትመንት ስም ሰፋፊ መሬትና የማዕድን ቦታ የያዙ አሉ። ህዝብ አነዚህ ኦሮሚያን እያለቡ ያሉትን ጠንቅቆ ያውቃቸዋል። በተለይም ንጹህ ህሊና ያላቸው ጉዳዩን ከነስሌቱ ይረዱታል። ከነዚህ "ባለጊዜዎች" ዝም ተብለው ምስኪ ጭሮ አዳሪዎች ላይ እንዲህ ያለው ተግባር መፈጸሙ ውሎ አድሮ ወዴት የሚያሰኝ ይሆናል። ነገም በስፋት በተለያዩ ስፋራዎች ድርጊቱ ስላለመቀጠሉ ዋስትና የለም። በሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ላይ።


እነዚህ ከጎንደር እንደመጡና ላለፉት 20 ዓመታት በስፍራው ላይ በህጋዊነት የሰፈሩት ወገኖች እነሱ ካሉት ውጪ ቦታው ላይ መኖር የማይችሉበት ህጋዊ አግባብ ካለ፣ ህጋዊ ጥፋት ወይም የመረጃ ችግር ካለባቸው በህግ ከሶና አስወስኖ አስፈላጊውን ውሳኔ ማሳለፍ ይቻላል። ህግና ስርዓት ባለበት አገር በትር በመንጠቅ ምስኪኖቸን በገጀራ ማስደብደብና ማስገደል ዘግናኝ ነው። ሰዎቹ እንዳሉት ሶስት ገበሬ ማህበር የሚሆኑ ናቸው። አንድ ገበሬ ማህበር ውስጥ ባማካይ 600 አባወራ አለ። በሶስት ሲባዛ የአባወራዎቹ ቁጥር ከፍተኛ ይሆናል። አሁንም እንሱ እንደገለጹት እያንዳዳቸው ባማካይ ስድስትና ሰባት ቤተሰብ አላቸው። እናም ጉዳዩ በቀላል የሚታይ አይሆንም።

“ አማራ በሚለው ደማችንና አጥንታችን አትውቀሱን" አልናቸው በማለት ሰዎቹ እንደገለጹት፣ ጥቃቱ የሚደርስባቸው በዘር ነው። ይህ ደግሞ ኢህአዴግ በተለይም ህወሃት የተከለው አጀንዳ ነው። ህወሃት በፕሮግራም ደረጃ አማራን የማትፋት እቅድ ይዞ ሲታገል የኖረ፣ አሁን ደግሞ ብአዴን የሚባል ላንቲካ/ ሲምቦል ድርጅት አስቀምጦ ይህንኑ የበታችነት ስጋቱ የፈጠረበትን ስሜት እያስተገበረ ነው። ብአዴን ውስጥ ያሉ ወገኖች ግን እስከመቼ በዚህ ይቀጥላሉ?
- ቪዲዮውን ከዚህ በታች አድምጡት

"መኖሬን ጠላሁት። ራሴን እንዳልገድል ወንጀል ነው። ሰው እንዳልገድል ወንጀል ነው" በሚል ግራ መጋባት አንድ አዛውንት ይናገራሉ። ተበዳዮች ከእርሻ ስራ በሁዋላ የሚይዙትን በትር ፖሊስ ሰበሰበ። ከዚያም እገበያ ቦታ ላይ ገጀራና ጦር የያዙ ጎረምሶች እየጮሁ ጥቃት መፈጸም ጀመሩ። 16 ሰዎች፣ 26 ናቸው የሚሉ አሉ ጉዳት ደረሰባቸው። አንደ ኢ ሰው ተገደሉ።

ይህ ዜና የተወሰደው ተበዳዬች ራሳቸው ባንደበታቸው ሲናገሩ ከሚታዩበት ቪዲዮ ነው። የተገደሉት አቶ ጌጡ ክብረት ይባላሉ። የሰባት ልጆች አባት ናቸው። የተገደሉት በገጀራ ነው። ከተገደሉ በሁዋላ አይናቸውን አውጥተዋቸዋል። አንደኛው ተናጋሪ አዛውንት እንደተናገሩት ደግሞ "ብልታቸውን ሸንሽነዋቸዋል"

ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ለህክምና ሲሄዱ " ሂድና አገርህ ታከም። ይህ የእኛ ሃኪም ቤት ነው" እንደተባሉ ምስክሮቹ ይናገራሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው በምዕራብ ሸዋ ዞን ደኖ ወረዳ በሶስት ቀበሌ ገበሬ ማህበራት በሚኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎች ላይ ነው።

ሰዎቹ እንደገለጹት ከጎንደር ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ነው ወደ ስፍራው የገቡት። በህጋዊ ማመልከቻና በህጋዊ የአስተዳደር አካላት ውሳኔ ቀደም ሲል የዝንጀሮ መንጋ የሚኖርበትን ስፋራ እንዳለሙ ይናገራሉ። በዚህም ላይ ህጋዊ ግብር የሚከፍሉ ናቸው። አንድ እንድሜያቸው የገፋ ተናጋሪ በቪዲዮው ላይ እንደተናገሩት " አስተዳደሩ ቻፓ መቶ" አስረክቧቸዋል።

ከሃያ ዓመታት በሁዋላ አሁን " አማርኛ ተናጋሪ ናችሁ። መሬቱን ለቃችሁ ውጡ" የተባሉት ሰዎች ለፌደራል ባለስልጣናት አቤቱታ ማቅረባቸው ይበልጥ ጉዳት አስከትሎባቸዋል። " እስኪ ምን ታመጣለህ" በሚል ያካባቢው አስተዳደር አካላት ቀልደውባቸዋል። ከሁሉም በላይ ግን ላለፉት ሃያ ዓመታት አብረዋቸው የኖሩ ሰዎች ዛሬ እንዴት ጨክነው ገጀራ አነሱ? የሚለው ጉዳይ ስጋት የሚጭር ሆኗል። በተለይም የፍትህ አካላትና ራሱ ኢህአዴግ፣ ብአዴን ሰው በገጀራ ሲገደል ዝም ማለታቸው ድርጊቱን አሳዛኝ ያደርገዋል።

በተለያዩ ክልሎች የተለያዩ ብሔረሰብ ተወላጆች አሉ። ተስማምተውና ተከባብረው ኖረዋል። አሁንም እየኖሩ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ከጥንት ጀምሮ ተዋልደው፣ ወልደውና ከብደው የኖሩ አማሮች ቁጥር ቀላል አይደለም። ኢህአዴግ አገር መግዛት ከጀመረ በሁዋላ ኦሮሚያ ላይ በኢንቨስትመንት ስም ሰፋፊ መሬትና የማዕድን ቦታ የያዙ አሉ። ህዝብ አነዚህ ኦሮሚያን እያለቡ ያሉትን ጠንቅቆ ያውቃቸዋል። በተለይም ንጹህ ህሊና ያላቸው ጉዳዩን ከነስሌቱ ይረዱታል። ከነዚህ "ባለጊዜዎች" ዝም ተብለው ምስኪ ጭሮ አዳሪዎች ላይ እንዲህ ያለው ተግባር መፈጸሙ ውሎ አድሮ ወዴት የሚያሰኝ ይሆናል። ነገም በስፋት በተለያዩ ስፋራዎች ድርጊቱ ስላለመቀጠሉ ዋስትና የለም። በሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ላይ።

እነዚህ ከጎንደር እንደመጡና ላለፉት 20 ዓመታት በስፍራው ላይ በህጋዊነት የሰፈሩት ወገኖች እነሱ ካሉት ውጪ ቦታው ላይ መኖር የማይችሉበት ህጋዊ አግባብ ካለ፣ ህጋዊ ጥፋት ወይም የመረጃ ችግር ካለባቸው በህግ ከሶና አስወስኖ አስፈላጊውን ውሳኔ ማሳለፍ ይቻላል። ህግና ስርዓት ባለበት አገር በትር በመንጠቅ ምስኪኖቸን በገጀራ ማስደብደብና ማስገደል ዘግናኝ ነው። ሰዎቹ እንዳሉት ሶስት ገበሬ ማህበር የሚሆኑ ናቸው። አንድ ገበሬ ማህበር ውስጥ ባማካይ 600 አባወራ አለ። በሶስት ሲባዛ የአባወራዎቹ ቁጥር ከፍተኛ ይሆናል። አሁንም እንሱ እንደገለጹት እያንዳዳቸው ባማካይ ስድስትና ሰባት ቤተሰብ አላቸው። እናም ጉዳዩ በቀላል የሚታይ አይሆንም።

“ አማራ በሚለው ደማችንና አጥንታችን አትውቀሱን" አልናቸው በማለት ሰዎቹ እንደገለጹት፣ ጥቃቱ የሚደርስባቸው በዘር ነው። ይህ ደግሞ ኢህአዴግ በተለይም ህወሃት የተከለው አጀንዳ ነው። ህወሃት በፕሮግራም ደረጃ አማራን የማትፋት እቅድ ይዞ ሲታገል የኖረ፣ አሁን ደግሞ ብአዴን የሚባል ላንቲካ/ ሲምቦል ድርጅት አስቀምጦ ይህንኑ የበታችነት ስጋቱ የፈጠረበትን ስሜት እያስተገበረ ነው። ብአዴን ውስጥ ያሉ ወገኖች ግን እስከመቼ በዚህ ይቀጥላሉ?
- ቪዲዮውን ከዚህ በታች አድምጡት